ሳምንቱን በአርብ

                                                                     
ከ http://theorthodoxchurch.info/blog/news/ የተወሰዱ የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት አንኳር ዜናዎች

  • ሰርቢያ /መጋቢት 18 2011/   የሰርቢያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ  ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ኤራንጂ በሰሜን አትላንቲክ ድርጅት /NATO/ ግድያ የተፈፀመባቸው የሰርቢያውያን መታሰቢያ ሥርዓት ቅዳሴ መርተዋል። ቅዱስነታችው በመታሰቢያ መርሃ ግብሩ ላይ ‘’ አባት ሃገራችንን እንጠብቃት፥ ያለን ብችኛ ጥንካሬም አንድንታችን ብቻ ነው።’’ ብለዋል።  


  • ሶሪያ /መጋቢት 18 2011/  የሶሪያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ  ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ኢግናጢዮስ ኤፍሬም II የብስራተ ድንግል ማርያምን በዓልና የሱቦሮ ቲቪ/SUBORO TV/ን የምረቃ በዓል ቅዳሴ መሩ። ቅዱስነታችው በዕለቱ በሰጡት ቃለ ምዕዳን ላይ “ከድንግል ማርያም በጌታ መታመንንና ሰማያዊ መልእክትን ለመክራ የሚያበቃን ቢሆንም እንኳን ምቀበልን ልንማር ይገባል።” ካሉ ብኋላ በመላው አለም ለሚገኙ የሶሪያ ኦርቶዶክሳዊያን በቴሌቪዠን ስርጭቱ መጀመር የእንኳን ደስ አላችሁ  መልእክታችውን አስተላልፈዋል።


  • አውስትራሊያ /መጋቢት 17 2011/  በአውስትራሊያ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሰታሊያኖስ አረፉ።



  • እንግሊዝ /መጋቢት 13 2011/ በእንግሊዝ የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ  ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አንጋሊዎስ የእንግሊዝ የቤቶች ጉዳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃሉን ትርጉም በማዛባት ለክርስቲያን ኢራናዊያን ጥገኘነት ፈላጊዎች የሰጠውን ምላሽ ተቃወሙ። ብፁዕነታቸው ቢሮው ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን የማየት መብት የለውም ብለዋል።


ሙሉ ንግግራቸውን ለማዳመጥ https://www.premier.org.uk/News/UK/Home-Office-withdraws-refusal-of-asylum-seeker-after-criticising-the-Bible-in-rejection-letter
  • እስራኤል/መጋቢት 19 2011/    የእስራኤሉ ፕሬዝዳንት ሪዩቫን ሪቫሊን ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ምሪዎች ጋር የዮርዳኖስ ወንዝን ባሀረ ጥምቀት ጎብኙ። በጉብኝቱ ላይ የምስራቅና የኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት አባቶች ተሳትፈዋል።



No comments:

Post a Comment