ከኦርቶዶክስ አንድነት ገጽ ሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ ለቅዱሳን ፓትሪያርኮች፣ ለብጹአን የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት እና ለቅድስት ቤ/ክ የተላለፈ መልእክት



የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ
28/10/2019
ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ
ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቀሪዮስ
እጅግ የተከበራችሁ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መንበረ ፓትሪያርክ
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ


የተከበራችሁ ቅዱሳን ፓትሪያሪኮችና የተወደዳችሁ ብጹአን የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት


ወንድማዊ ሰላምታችን ይድረሳችሁ፡

ይህን አጋጣሚ በመጠቀም በኢትዮጵያ እየሆነው ያለው ነገር በከፍተኛ መጠን እያሳሰበኝ መሆኑን ለመግለጽ እፈልጋለሁ፡፡ ሁኔታዎችን በቅርብ እየተከታተልን በ ኦሲፒ ሚዲያ ነ አማካኝነት በቤተ ክርስቲያኒቷ ልጆች ላይ እየደረሱ ስላሉ ጥቃቶች የተለያዩ ዜናዎችንና ዘገባዎችን እየሰራን ሲሆን የተባበሩትን መንግስታት ጨምሮ ወደ ተለያዩ የሰብአዊ መብት ተቋማት የሚላኩ የፊርማ ማሰባሰቢያዎችን እየሞላን እንገኛለን፡፡

እግዚአብሔር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን፣ አመራሯን እና ምእመናኗን ከዚህ ችግር እንድትወጡ ያበርታችሁ፡፡ ጌታችንና አምላካችን ቤተክርስቲያንን ይጠብቅ፡፡ በኢትዮጵያም ላይ ሰላምና ብልጽግና እንዲመጣ ክብሩን ይግለጥ፡፡
እ.ኤ.አ በ2013 ለጸሃፊያችን ጆርጅ አሌክሳንደር በኢትየጵያ በመንበረ ፓትሪያርክ ላደረጋችሁለት አቀባበል እያመሰገንን በ ኢ.አ በ2016 እርሶን በህንድ በመንበረ ፓትሪያርኳ ኮታየም ኬርላ እርሶን /ብ.ወቅ. አቡነ ማትያስ/ በመቀበላችን የተሰማንን ደስታ ለመግለፅ ዳለን፡፡ሁሌም ከናንተ ጋር ነን፡፡ 

   
በክርስቶስ ሰላም


ጆርጅ ጆሴፍ

ሊቀ መንበር

ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልልና በአካባቢዎቹ በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስቲያኖች ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶችን አስመልክቶ የኦርቶዶክስ አንድነት ገጽ /Orthodox cognate pafe (OCP)/ ለተባበሩት መንግስታት፣ ለአሜሪካ መንግስት የሃይማኖቶች ነጻነት ተቋምና ለተለያዩ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ሪፖርቶችን አቀረበ፡፡



በኦርቶዶክሳዊያን አንድነትና አለማቀፋዊ ትብብር ዙሪያ የሚሰራው የኦርቶዶክስ አንድነት ገጽ አለማቀፋዊ ተቀባይነቱ ከፍተኛ በሆነው ድረ ገጹ theorthodoxchurch.info በተከታታይ የኢትዮጵያውያን ኦርቶዶክሳውያንን ጥቃት በመዘገብ ለአለም ኦርቶዶክሳዊያን ማህበረሰብ በማሳወቅ  ላይ የሚገኘው  የኦርቶዶክስ አንድነት ገጽ በዚህ ሳምንት የተባበሩት መንግስታትን ጨምሮ  ከዚህ በታች ለተዘረዘሩ የአለም የሰብአዊ መብት ተቋማት የጉዳዩን አሳሳቢነት የሚተነትን ሪፖርት ማስገባቱን የተቋሙ ሰክሬተሪያት ጂኦርጅ አሌክሳንደር ዛሬ ለ ተቋሙ የአማርኛ አገልግሎት OCPamharic ተናግረዋል   


The Office of the United Nations High Commissioner for Human Rights

President of the Russian Federation 

Prime Minister of Hungary

Chancellor of Germany

African Commission on Human and Peoples’ Rights

The U.S. Commission on International Religious Freedom

Organization for Security and Co-operation in Europe (OSCE)

UNESCO

Conference of European Churches

Churches Together in England

The Archbishop of Canterbury 

The Anglican Communion

Lutheran World Federation

Global Christian Forum

Release International

International Christian Concern

Christian Solidarity International

The Voice of the Martyrs

Justice Revival

Christian Solidarity Worldwide

Stefanus Alliance International

Human Rights Watch

Amnesty International

በትናንትናው እለት ቅዱስ ሲኖዶስ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ለሰማዕታቱ ጸሎተ ፍትሃት ማካህዱ የሚታወስ ነው፡፡





የሃይማኖት ጸሎት /The Creed - የኦርቶዶክሳዊያን አለማቅፋዊ የጋራ ጸሎት


 

ኹሉን በያዘ፣ ሰማይንና ምድርን፥ የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ፡ አንድ አምላክ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን።
ዓለም ሳይፈጠር፡ ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ አንድ የአብ ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን። እርሱም፡ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፥ የተወለደ እንጂ፡ ያልተፈጠረ፣ በመለኮቱ፡ ከአብ ጋራ የሚተካከል፣ ኹሉ፡ በእርሱ የኾነው፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በሰማይ ካለው፣ በምድርም ካለው፡ ያለእርሱ፡ ምንም ምን፡ የኾነ የለም።
ስለእኛ ስለሰዎች፥ እኛን ለማዳን፡ ከሰማይ ወረደ፤ በመንፈስ ቅዱስ ግብር፡ ከቅድስት ድንግል ማርያም፡ ከሥጋዋ፡ ሥጋ፥ ከነፍሷ፡ ነፍስ ነሥቶ፡ ፍጹም ሰውን ኾነ። በጴንጤናዊው ጲላጦስ ዘመን፡ ስለእኛ፡ መከራን ተቀበለ። ተሰቀለ። ሞተ። ተቀበረ። በሦስተኛውም ቀን፡ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። በክብር፥ በምስጋና፡ ወደሰማይ ዐረገ። በአባቱም ቀኝ፡ በዙፋኑ ተቀመጠ። ዳግመኛም፡ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ፡ በምስጋና ይመለሳል። ለመንግሥቱ፡ ፍጻሜ የለውም።
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም እናምናለን። እርሱም፡ ሕይወትን የሚሰጥ፣ ከአብ የሠረፀና በነቢያት ዐድሮ የተናገረው፥ በሓዋርያት ላይ የወረደውና በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት፡ ዓለሙን፡ በጸጋው የሞላው፡ ቅዱሱ የእውነት መንፈስ ነው። ለእርሱም፡ ከአብና ከወልድ ጋራ፡ በአንድነት እንሰግድለታለን፤ እናመሰግነዋለንም።
በአንዲት ቅድስት ካቶሊክ እና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።
ኃጢኣት በሚሠረይባት፡ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን።
በሙታን ትንሣኤ፥ በዘለዓለምም ሕይወት እናምናለን። ለዘለዓለሙ፤ አሜን።

የኦርቶዶክስ አንድነት ገጽ ማህበር አመሰራረት


የኦርቶዶክስ አንድነት ገጽ ማሀበር የኦርቶዶከሰ እምነትንና አንድነትን ለማስተዋውቅ በህንድ ሃገር በTravancore-Cochin Literary, Scientific and Charitable Societies Registration Act of 1955 መሰረት  እ.ኢ.አ በሰኔ/ሐምሌ 2007 ወሰን የለሽ ኦርቶዶከስ በሚል ስያሜ ተመሰረተ፡፡ በ2010ም ስሙን አሁን ወደሚጠራበት የኦርቶዶክስ አንድነት ገጽ ለወጠ፡፡
ተቋሙ ለምስራቃዊያንና ለኦሪየንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት እኩል ትኩረት የሚሰጥ ሲሆን ሁለቱም አብያተ ክርስቲያናት የሐዋሪያትና የቅዱሳን አባቶችና እናቶች እምነት የነበረችው የአንዲት ቅድስት ክብርት አለማቀፋዊት(ካቶሊካዊት)ና ሃዋሪያዊት የሆነች የክርስቶስ ቤተ ክርሰቲያን አካላት ናቸው ብሎ ያምናል፡፡ መሪ ቃሉም የተባበሩት የኦርቶዶክሳዊያን ክርስቲያኖች ምስክር የሆነውም በዚህ መነሻነት ነው፡፡
ተቋሙ አስቀድሞ ለሁለቱ የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት የዜና ምንጭ ሆኖ ማገልገልን አላማው አድርጎ በሊቀ መንበር፣ ምክትል ሊቀ መንበርና ጸሐፊ ሲመራ የነበረ ሲሆን በ2010 እ.ኤ.አ ግን ከስያሜ ለውጥ ባሻገር የአደረጃጀት ለውጥ በማድረግ 10 አመራሮች ባሉት ቦርድ መመራት ጀመረ፡፡ እንደ አንድ ህጋዊ ተቋምነቱ በየሶስት አመቱ የሚመረጥ አንድ አንድ መራሂ፣ ሊቀ መንበር፣ ምክትል ሊቀ መንበር፣ ጸሐፊና አምስት አባላት ያሉት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ያለው ሲሆን ከሱ በታች ደግሞ ኦሲፒ ፋውንዴሽን፣ የመልዕክተኞች ጉባኤ፣ ጽህፈት ቤቱ፣ መምሪያዎችና የታዛቢዎች ጉባኤ በቅደም ተከተል አሉት፡፡
ተቋሙ የዜናና ጋዜጠኝነት፣ የጥናትና ምርምር፣ የማህበራዊ ሰብአዊ ድጋፎች፣ የጉብኝትና ውይይቶች፣ የዕውቅና አሰጣጥ፣ ንቅናቄዎችን የማዘጋጀትና ኦርቶዶክሳዊ ልኡካንን የመደገፍእንቅስቃሴዎችን ያካሂዳል፡፡
የተቋሙ መልክተኞች በተለያዩ ጊዜያት ከተለያዩ የኢርዶከስ አብያተ ክርስቲያት መሪዎች ጋር ተገናኝተው በአላማው ዙሪያ ተወያይተው  አወንታዊ ምላሾችን ከማግኘት ባሻገር የመታሰቢያ ሥጦታዎችን አበርክተዋል፡፡ ለአብነት ያህልም በፌብሩዋሪ 2008 የእንግሊዝ የኮብቲክ ኦርቶዶከስ ሊቀ ጳጳስ አባ ሱራፌል/ሴራፒም/ን ና ልኡካኑን፣ በ2010ና 2011 ከሶሪያ ኦርቶዶከስ ቤተክርስቲያን ተወካዮችና በ2015 ከቅዱስ ፓትሪያሪኩ ብፁዕ ወቅዱስ ሞራን ሞር ኢግናጢዮስ ዘካ ጋር፣ በ2013 ከኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ፓትሪያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስና ከወቅቱ የቤተክርስቲያኗ ልማትና ተራድኦ ኮሚሽን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሳሙኤል ጋር፣ በተመሳሳይ በዛው አመት  ከግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የአክሱም ሊቀ ጳጳስ አቡነ ጴጥሮስ ጋር በ2014 ከኦሪየንታል አብያተ ክርስቲየናት ተወካዮች ጋር በህንድ፣ በ2015 ከህንድ ኦርቶዶክስ ፓትሪያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስሊዮስ ጳውሎስ 2ኛ እንዲሁም በ2015 ከሲሪዮ ኦርቶዶክሲ ፍራንክፎን ቤተክርስቲያን መሪ ከብፁዕ ሞር ማሪያም ፊሊጶስ ጋር ተገናኝተዋል


ሳምንቱን በአርብ

                                                                     
ከ http://theorthodoxchurch.info/blog/news/ የተወሰዱ የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት አንኳር ዜናዎች

  • ሰርቢያ /መጋቢት 18 2011/   የሰርቢያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ  ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ኤራንጂ በሰሜን አትላንቲክ ድርጅት /NATO/ ግድያ የተፈፀመባቸው የሰርቢያውያን መታሰቢያ ሥርዓት ቅዳሴ መርተዋል። ቅዱስነታችው በመታሰቢያ መርሃ ግብሩ ላይ ‘’ አባት ሃገራችንን እንጠብቃት፥ ያለን ብችኛ ጥንካሬም አንድንታችን ብቻ ነው።’’ ብለዋል።  


  • ሶሪያ /መጋቢት 18 2011/  የሶሪያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ  ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ኢግናጢዮስ ኤፍሬም II የብስራተ ድንግል ማርያምን በዓልና የሱቦሮ ቲቪ/SUBORO TV/ን የምረቃ በዓል ቅዳሴ መሩ። ቅዱስነታችው በዕለቱ በሰጡት ቃለ ምዕዳን ላይ “ከድንግል ማርያም በጌታ መታመንንና ሰማያዊ መልእክትን ለመክራ የሚያበቃን ቢሆንም እንኳን ምቀበልን ልንማር ይገባል።” ካሉ ብኋላ በመላው አለም ለሚገኙ የሶሪያ ኦርቶዶክሳዊያን በቴሌቪዠን ስርጭቱ መጀመር የእንኳን ደስ አላችሁ  መልእክታችውን አስተላልፈዋል።


  • አውስትራሊያ /መጋቢት 17 2011/  በአውስትራሊያ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሰታሊያኖስ አረፉ።



  • እንግሊዝ /መጋቢት 13 2011/ በእንግሊዝ የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ  ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አንጋሊዎስ የእንግሊዝ የቤቶች ጉዳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃሉን ትርጉም በማዛባት ለክርስቲያን ኢራናዊያን ጥገኘነት ፈላጊዎች የሰጠውን ምላሽ ተቃወሙ። ብፁዕነታቸው ቢሮው ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን የማየት መብት የለውም ብለዋል።


ሙሉ ንግግራቸውን ለማዳመጥ https://www.premier.org.uk/News/UK/Home-Office-withdraws-refusal-of-asylum-seeker-after-criticising-the-Bible-in-rejection-letter
  • እስራኤል/መጋቢት 19 2011/    የእስራኤሉ ፕሬዝዳንት ሪዩቫን ሪቫሊን ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ምሪዎች ጋር የዮርዳኖስ ወንዝን ባሀረ ጥምቀት ጎብኙ። በጉብኝቱ ላይ የምስራቅና የኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት አባቶች ተሳትፈዋል።



የመጽሔት ግብዣ

https://basilica.ro/wp-content/uploads/2019/03/The-Good-to-Know-March-2019.pdf

የኦርቶዶክስ የአንድት ገፅ /OCP/ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ

theorthodoxchurch.info
መግቢያ
የአለም አብያተክርስቲያናት በአንዲት ፣ሃዋርዊት ና አለምአቀፋዊት አንድነት ውስጥ ሣይከፋፈሉ ና ሣይነጣጠሉ ለመቆየት የታደሉት ከግማሽ ሺህ ዘመን ላልበለጠ ጊዜ ነበር።
አብያተክርስቲያናቱ ለ400 አመታት የገጠማቸውን የሠማዕትነት ዘመን አልፈው የክርስትናው ሀይማኖት በስፋት መግለጥ ፣ማብራራት ፣ ማስተማር ና መመርመር /ማመስጠር/ በጀመሩበት ዘመን ምንፍቅና ፣ ልዩልዩ የአስተምህሮ ልዩነት ፣ አለማዊ ፍልስፍና ቅየጣ እንዲሁም ፈተናዎች የክርስቶስ ቤተከርስቲያንን ያናውጣት ጀመር፡፡ በዚያ ዘመን እነዚህን ችግሮች ቢቻል ለመፍታት ባይቻል የችግሩን አካላት ለመለየት የተለያዩ አለምአቀፍ ጉባዔዎች ተካሂደዋል፡፡ ከነዚህ መካከል 4ቱ ጉባኤያት ይጠቀሳሉ፡፡ 3ቱ በእሪየንታል /የተዋህዶ/ ና ምሥራቅ ኦርቶዶክስ ና የካቶሊክ አብያተክርስቲያናት ተቀባይነት ሲኖራቸው 4ተኛው እና የመከፋፈል ምክንያት የሆነው ጉባዔ ግን በኦሪየንታል/የተዋህዶ / አብያተክርስቲያናት ተቀባይነት ያላገኘና ከምስራቅ /የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ና የካቶሊክ / አብያተክርስቲያናት ጋር በመወጋገዝ ያለያየ ና አብያተክርስቲያናት የተከፋፈሉበት ነበር፡፡
ይህ ዘመን ካለፈ በሗላ እጅግ በርካታ መከፋፈሎች ና ግጭቶች በተመሣሣይ ሁኔታ ደግሞ ወደ አንድነት ለመምጣት የሚደረጉ ጥረቶችም በዚሁ መልኩ ቀጥለዋል፡፡
 በተለይም በሁለቱ የኦርቶዶክስ አብያተክርስቲያናት መካከል በተከታታይ የተደረጉ ይፋዊ ና ህቡዕ ውይይቶች አብያተክርስቲያናቱ እንዲቀራረብ ና አንድ የመሆን የመሆን ስሜቶች የተፈጠሩበት ወቅት ነበር፡፡
ለአብነትም 7ቱን የነገረ መለኮት ውይይቶች ማንሳት ይቻላል፡፡ እነሱም
1/ አርሁስ ፣ ዴንማርክ /ከነሃሴ 11 - 15 1964/
2/ ብሪስተል ፣ ኢንግላንድ /ከነሃሴ 25 - 29 1967/
3/ ጄኔቫ ፣ ስዊዘርላንድ /ከነሃሴ 16 - 21 1970/
4/ አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ /ከጥር 22 - 23 1971/
5/ አባ ቢሾይ ገዳም ፣ ግብፅ /1989/
6/ ቻምባዚ ፣ ስዊዘርላንድ /1990/
7/ ቻምባዚ ፣ ስዊዘርላንድ /1993/ በነገረ ክርስቶስ /Christology) ዙሪያ መግባባት የተደረሠበትና አውጣኪና ንስጥሮስን የሚያወግዟቸው መሆኑን ያስረገጡበት ና ለመቀራረቦች በር የከፈተው ጉባኤ )
* ሁሉም አቆጣጠሮች እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ነው፡፡
ስለሁለቱ የኦርቶዶክስ ቤተሠቦች ይህን ያሀል ካየን ስለ የኦርቶዶክስ አንድነት ገፅ/OCP/
አመሠራረት ና ሌሎች ጉዳዮች በሚቀጥለው ክፍል እናነሣለን፡፡